×

Surah Al-Mutaffifin in Amharic

Quran Amharic ⮕ Surah Mutaffifin

Translation of the Meanings of Surah Mutaffifin in Amharic - الأمهرية

The Quran in Amharic - Surah Mutaffifin translated into Amharic, Surah Al-Mutaffifin in Amharic. We provide accurate translation of Surah Mutaffifin in Amharic - الأمهرية, Verses 36 - Surah Number 83 - Page 587.

بسم الله الرحمن الرحيم

وَيْلٌ لِّلْمُطَفِّفِينَ (1)
ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡
الَّذِينَ إِذَا اكْتَالُوا عَلَى النَّاسِ يَسْتَوْفُونَ (2)
ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡
وَإِذَا كَالُوهُمْ أَو وَّزَنُوهُمْ يُخْسِرُونَ (3)
ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡
أَلَا يَظُنُّ أُولَٰئِكَ أَنَّهُم مَّبْعُوثُونَ (4)
እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን
لِيَوْمٍ عَظِيمٍ (5)
በታላቁ ቀን፡፡
يَوْمَ يَقُومُ النَّاسُ لِرَبِّ الْعَالَمِينَ (6)
ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡
كَلَّا إِنَّ كِتَابَ الْفُجَّارِ لَفِي سِجِّينٍ (7)
በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡
وَمَا أَدْرَاكَ مَا سِجِّينٌ (8)
ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ
كِتَابٌ مَّرْقُومٌ (9)
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ (10)
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
الَّذِينَ يُكَذِّبُونَ بِيَوْمِ الدِّينِ (11)
ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡
وَمَا يُكَذِّبُ بِهِ إِلَّا كُلُّ مُعْتَدٍ أَثِيمٍ (12)
በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡
إِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِ آيَاتُنَا قَالَ أَسَاطِيرُ الْأَوَّلِينَ (13)
አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
كَلَّا ۖ بَلْ ۜ رَانَ عَلَىٰ قُلُوبِهِم مَّا كَانُوا يَكْسِبُونَ (14)
ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡
كَلَّا إِنَّهُمْ عَن رَّبِّهِمْ يَوْمَئِذٍ لَّمَحْجُوبُونَ (15)
ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡
ثُمَّ إِنَّهُمْ لَصَالُو الْجَحِيمِ (16)
ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡
ثُمَّ يُقَالُ هَٰذَا الَّذِي كُنتُم بِهِ تُكَذِّبُونَ (17)
ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡
كَلَّا إِنَّ كِتَابَ الْأَبْرَارِ لَفِي عِلِّيِّينَ (18)
በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡
وَمَا أَدْرَاكَ مَا عِلِّيُّونَ (19)
ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ
كِتَابٌ مَّرْقُومٌ (20)
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
يَشْهَدُهُ الْمُقَرَّبُونَ (21)
ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡
إِنَّ الْأَبْرَارَ لَفِي نَعِيمٍ (22)
እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡
عَلَى الْأَرَائِكِ يَنظُرُونَ (23)
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡
تَعْرِفُ فِي وُجُوهِهِمْ نَضْرَةَ النَّعِيمِ (24)
በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡
يُسْقَوْنَ مِن رَّحِيقٍ مَّخْتُومٍ (25)
ተጣርቶ ከታተመ ጠጅ ይጠጣሉ፡፡
خِتَامُهُ مِسْكٌ ۚ وَفِي ذَٰلِكَ فَلْيَتَنَافَسِ الْمُتَنَافِسُونَ (26)
ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡
وَمِزَاجُهُ مِن تَسْنِيمٍ (27)
መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡
عَيْنًا يَشْرَبُ بِهَا الْمُقَرَّبُونَ (28)
ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡
إِنَّ الَّذِينَ أَجْرَمُوا كَانُوا مِنَ الَّذِينَ آمَنُوا يَضْحَكُونَ (29)
እነዚያ ያምመጹት በእነዚያ ባመኑት በእርግጥ ይስቁ ነበሩ፡፡
وَإِذَا مَرُّوا بِهِمْ يَتَغَامَزُونَ (30)
በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡
وَإِذَا انقَلَبُوا إِلَىٰ أَهْلِهِمُ انقَلَبُوا فَكِهِينَ (31)
ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ ነበር፡፡
وَإِذَا رَأَوْهُمْ قَالُوا إِنَّ هَٰؤُلَاءِ لَضَالُّونَ (32)
ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡
وَمَا أُرْسِلُوا عَلَيْهِمْ حَافِظِينَ (33)
በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡
فَالْيَوْمَ الَّذِينَ آمَنُوا مِنَ الْكُفَّارِ يَضْحَكُونَ (34)
ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡
عَلَى الْأَرَائِكِ يَنظُرُونَ (35)
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡
هَلْ ثُوِّبَ الْكُفَّارُ مَا كَانُوا يَفْعَلُونَ (36)
ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡
❮ Previous Next ❯

Surahs from Quran :

1- Fatiha2- Baqarah
3- Al Imran4- Nisa
5- Maidah6- Anam
7- Araf8- Anfal
9- Tawbah10- Yunus
11- Hud12- Yusuf
13- Raad14- Ibrahim
15- Hijr16- Nahl
17- Al Isra18- Kahf
19- Maryam20- TaHa
21- Anbiya22- Hajj
23- Muminun24- An Nur
25- Furqan26- Shuara
27- Naml28- Qasas
29- Ankabut30- Rum
31- Luqman32- Sajdah
33- Ahzab34- Saba
35- Fatir36- Yasin
37- Assaaffat38- Sad
39- Zumar40- Ghafir
41- Fussilat42- shura
43- Zukhruf44- Ad Dukhaan
45- Jathiyah46- Ahqaf
47- Muhammad48- Al Fath
49- Hujurat50- Qaf
51- zariyat52- Tur
53- Najm54- Al Qamar
55- Rahman56- Waqiah
57- Hadid58- Mujadilah
59- Al Hashr60- Mumtahina
61- Saff62- Jumuah
63- Munafiqun64- Taghabun
65- Talaq66- Tahrim
67- Mulk68- Qalam
69- Al-Haqqah70- Maarij
71- Nuh72- Jinn
73- Muzammil74- Muddathir
75- Qiyamah76- Insan
77- Mursalat78- An Naba
79- Naziat80- Abasa
81- Takwir82- Infitar
83- Mutaffifin84- Inshiqaq
85- Buruj86- Tariq
87- Al Ala88- Ghashiya
89- Fajr90- Al Balad
91- Shams92- Lail
93- Duha94- Sharh
95- Tin96- Al Alaq
97- Qadr98- Bayyinah
99- Zalzalah100- Adiyat
101- Qariah102- Takathur
103- Al Asr104- Humazah
105- Al Fil106- Quraysh
107- Maun108- Kawthar
109- Kafirun110- Nasr
111- Masad112- Ikhlas
113- Falaq114- An Nas